"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Tuesday 9 April 2013

ደራሲ በአሉ ግርማ በባህርዳር ጣና ሐይቅ ዙሪያ አለም በቃኝ ብሎ ሞንኩሶ እግዚአብሄርን እያገለገለ መሆኑ ታወቀ !!!

22
ዛሬ ማምሻውን ከወደ ባህርዳር አካባቢ የተሰማው ወሬ በርካቶችን እያስገረመ እና እያስደነገጠ ይገኛል፡፡በርካታ ኢትዮጲያውያን በእጅጉ የሚያደንቁት፣ ነገር ግን በደርግ መንግስት ታፍኖ የደረሰበት  ያልታወቀው ደራሲ በአሉ ግርማ በባህርዳር ጣና ሐይቅ ዙሪያ ከሚገኙ ደሴቶች አንዱ በሆነው የዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ውስጥ አለም በቃኝ ብሎ ሞንኩሶ እግዚአብሄርን እያገለገለ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ቀደም ሲል በይስማእከ ወርቁ ደራሲነት የምናውቃቸው ዴርቶጋዳ፣ራማቶሃራ፣ዣንዥድ እና ተልሚድ የተሰኙ ስራወች የደራሲ በአሉ ግርማ መሆናቸው እና በይስማዕከ ወርቁ አማካኝነት የወጡ መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡ይሄ ወሬ ከተሰማ በኋላ በርካታ የባህርዳር ነዋሪወች የዳጋ ደሴትን ያጨናነቁ ሲሆን የአዲስአበባና የሌሎች የሃገራችን ክፍል ነዋሪዎችም ነገ በማለዳ ወደ
ባህርዳር ጉዞ ለማድረግ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ መኪና እና የፕሌን ትኬቶች ተሽጠው ያለቁ ሲሆን የኢትዮጲያ አየር መንገድም ነግ እና ከነገ በስቲያ ወደ ሌሎች የሃገራችን ክፍሎች የሚደረጉ በረራዎችን ሰርዞ ጉዞ ወደ ባህርዳር ብቻ እንደሚያደርግ ተነግሯል

2 comments: